የሰፈር የመደብር ሱቅ ፕሮጀክት (NEIGHBORHOOD STOREFRONTS PROJECT)

የፕሮጀክቱ አውድ እና ግቦች

አነስተኛ የችርቻሮ ንግድ ስራዎች የረጅም ጊዜ ስኬትን በማሳካት ረገድ ብዙ ፈተናዎች ያጋጥሟቸዋል። ከተለመዱ ተግዳሮቶች መካከል የካፒታል አቅርቦት እጦት፣ የንግድ ሥራ ድጋፍ ግብዓቶች እጥረት እና በየጊዜው እየተለወጠ የመጣው የችርቻሮ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥን ያካትታል።

በ Cambridge ውስጥ፣ በተለይ ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው የችርቻሮ ንግድ ቦታ አለመኖር ትልቅ እንቅፋት ነው።

የስትራቴጂክ እቅዱ መርሀ ግብር፣ የ Cambridge Redevelopment Authority’s Neighborhood Storefronts Project (የ Cambridge ማሻሻያ ባለስልጣን የሰፈር ፊት ለፊት ሱቆች ፕሮጀክት) አላማ ለአነስተኛ ንግዶችን እና ለስራ ፈጣሪዎች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው ቦታዎችን በማቅረብ ድጋፍ ማድረግ ነው። ለተመጣጣኝ የችርቻሮ ቦታ አዲስ ሞዴል በማዘጋጀት የመርሀ-ግብሩ ዓላማዎች እንደሚከተለው ነው፦

  • በ Cambridge ውስጥ ተመጣጣኝ የችርቻሮ ቦታዎችን በማገናኘት የቢዝነስ ድጋፍ አገልግሎቶች መዳረሻ ያላቸውን የመሬት ወለል ቦታዎችን ፈልጎ ማግኛት

  • በ BIPOC፣ በሴቶች እና በስደተኛ ቡድኖች ባለቤትነት እና በእነሱ ስር ባሉ ላይ አፅንዖት በመስጠት የ Cambridge አነስተኛ ንግዶችን የረጅም ጊዜ ስኬትን መደገፍ


ተዛማጅ ሰነዶች


የመገኛ አድራሻ

ስለ Neighborhood Storefronts Project (የሰፈር መደብር ሱቅ ፕሮጀክት) ጥያቄዎች፣ እባክዎን ያነጋግሩ፦

ጆሽዋ ክሮም፣ የፕሮጀክት እቅድ አውጪ፦ jcroom@cambridgeredevelopment.org